Saturday, 11 May 2019 12:28

“ያልታመመ አዕምሮን እንዴት ማከም ይቻላል” የኪነ-ጥበብ ምሽት ሰኞ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 ሰምና ወርቅ ሚዲያና ኢንተርቴይመንት “ያልታመመ አዕምሮን እንዴት ማከም ይቻላል” የተሰኘ የኪነ-ጥበብ ምሽት ከነገ በስቲያ ሰኞ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ያካሂዳል፡፡ በምሽቱም ኢ/ር ወንድሙ ነጋሽ (ከእንግሊዝ)፣ ዶ/ር ብርሃኑ ኃ/ሚካኤል፣ ዶ/ር አበባየሁ ንጉሴ፣ መጋቢ ሀዲስ እሸቱ ዓለማየሁ፣ ሎሬት የትነበርሽ ንጉሴ፣ የፍልስፍና መምህሩ ዮናስ ዘውዴ፣ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ፣ መምህርት እፀገነት ከበደ ስራዎቻቸውን የሚያቀርቡ ሲሆን ገጣሚያኑ ኤፍሬም ስዩም፣ በቃሉ ሙሉ፣ ኤልያስ ሽታሁንና ህሊና ደሳለኝ በባህል ባንድ ታጅበው ግጥሞቻቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጿል፡፡

Read 2130 times