Print this page
Thursday, 09 May 2019 00:00

ጆርጅ ዊሃ በእባቦች ሳቢያ ወደተወው ቢሮው ተመልሷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የቀድሞው የአለማችን ኮከብ እግር ኳስ ተጫዋች፣ የላይቤሪያው ፕሬዚዳንት ጆርጅ ዊሃ፣ ከሁለት ሳምንታት በፊት በቢሮው ውስጥ ሁለት እባቦች መገኘታቸውን ተከትሎ፣ ወደ ቢሮው መግባት አቁሞ የነበረ ሲሆን ረቡዕ ዕለት ወደ ቢሮው መመለሱ ተዘግቧል፡፡
ከሁለት ሳምንታት በፊት የፕሬዚዳንቱ ቢሮ በሚገኝበት ህንጻ ውስጥ ሁለት አደገኛ እባቦች መገኘታቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ በአካባቢው የነበሩ ሰዎች እባቦቹን ለመግደል ጥረት ቢያደርጉም እንዳመለጧቸውና ተመልሰው ይመጣሉ በሚል ስጋት ፕሬዚዳንቱ ቢሯቸውን ትተው፣ በሌላ ክፍል ውስጥ ስራቸውን ሲሰሩ መሰንበታቸውንም አመልክቷል፡፡
ወደ ፕሬዚዳንቱ ቢሮ የመጡት ሁለት ጥቋቁር እባቦች፣ እጅግ መርዘኛና አደገኛ እንደሆኑ የጠቆመው ዘገባው፤ ጆርጅ ዊሃ ወደ ቢሯቸው እንዲመለሱ ከመደረጋቸው በፊት እባቦችን የሚያባርርና ኢንፌክሽንን የሚከላከል መድሃኒት በህንጻው ዙሪያ መረጨቱንም ገልጧል፡፡

Read 1093 times
Administrator

Latest from Administrator