Print this page
Saturday, 13 April 2019 14:03

ፌስቡክ የሞቱ ተጠቃሚዎቹን አካውንት ለመዝጋት አስቧል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ታዋቂው ማህበራዊ ድረገጽ ፌስቡክ ከዚህ አለም በሞት የተለዩ የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን አካውንት የሚዘጋበት አዲስ አሰራር እየቀየሰ መሆኑን ከሰሞኑ ባወጣው መረጃ አስታውቋል፡፡
በሞት የተለዩዋቸውን ዘመድ ወዳጅ እንዲሁም ጓደኞቻቸውን በተመለከተ በሚደርሷቸው የተለያዩ የፌስቡክ ኖቲፊኬሽኖች ወይም መልዕክቶች ሀዘናቸው ዳግም እየተቀሰቀሰባቸው መማረራቸውን የሚገልጹለት የፌስቡክ ተጠቃሚ ደንበኞቹ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉን ተከትሎ፣ ኩባንያው ችግሩን ለመፍታት ሲል የሟች ደንበኞቹን አካውንት የሚዘጋበት አዲስ አሰራር መቀየሱን ገልጧል፡፡
አንድ የፌስቡክ ተጠቃሚ በሞት ከተለየ በኋላ የፌስቡክ አካውንቱ እንደማይዘጋና፣ ለሌሎች የፌስቡክ ወዳጆቹም ሆነ ለሌላ ተጠቃሚ እንደሚታይ ያስታወሰው ኩባንያው፣ ከዚህ በኋላ ግን ጥቆማዎችን በመቀበልና አርቴፌሻል ኢንተለጀንስን በመጠቀም የሟቾችን አካውንት እያጣራ እንደሚዘጋ አመልክቷል፡፡

Read 1072 times
Administrator

Latest from Administrator