“ግጥም በበገና” አምስተኛ ዙር የስነ ፅሁፍ ምሽት የፊታችን አርብ በአዲስ አበባ ቴአትርና ባህል አዳራሽ እንደሚካሄድ ኢጋ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን አስታወቀ፡፡ በምሽቱ የበገና ድርደራ፣ የክራር ገረፋ፣ ግጥም፣ ህብረ ዝማሬ፣ ግለ ወግና የተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶች እንደሚቀርቡ ታውቋል፡፡ ኢጋ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን የህፃናትና የአዋቂ የንባብ ባህልን በማዳበር፣ ባህላዊና አገራዊ እሴቶችን በማጉላትና በተለያዩ የማንነታችን መገለጫዎቻችን እንድንኮራ የሚያደርጉ ፋይዳ ያላቸውን ስራዎች በመስራት የሚታወቅ ድርጅት ነው፡፡
Saturday, 13 April 2019 13:55
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና