Saturday, 06 April 2019 15:52

ኢቦላ በኮንጎ ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከስምንት ወራት በፊት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በአዲስ መልክ የተቀሰቀሰው የኢቦላ ወረርሽኝ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት እየተስፋፋ እንደሚገኝ የአለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡
ድርጅቱ በሳምንቱ መጀመሪያ ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ እንዳለው፣ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በአገሪቱ በሳምንት 75 ያህል አዳዲስ የኢቦላ ቫይረስ ተጠቂዎች መገኘታቸውንና ይህም ከዚህ ቀደም ያልታየና ከፍተኛ መሆኑን ገልጧል፡፡
በአገሪቱ በአስከፊነቱ በሁለተኛ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ የተነገረለትንና ከስምንት ወራት በፊት የተከሰተውን የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ያስታወሰው ድርጅቱ፣ የአዳዲስ ታማሚዎች ቁጥር እያደገ መምጣቱ ይህንን ጥረት እንዳያደናቅፈው ያሰጋል ብሏል፡፡
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በአዲስ መልክ የተቀሰቀሰው ይህ የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ 676 ያህል የአገሪቱ ዜጎችን ለሞት እንደዳረገ የጠቆመው ድርጅቱ፤ ኢቦላ እ.ኤ.አ ከ2013-16 በነበሩት አመታት በምዕራብ አፍሪካ አገራት በድምሩ ከ11 ሺህ በላይ ሰዎችን ለህልፈተ ህይወት መዳረጉንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1228 times