Print this page
Saturday, 06 April 2019 15:50

በናይሮቢ ከ75 በመቶ በላይ መጠጥ ቤቶች ሊዘጉ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በከተማዋ ከ12,500 በላይ መጠጥ ቤቶች ይገኛሉ

          የኬንያ ርዕሰ መዲና ናይሮቢ በከተማዋ ውስጥ አገልግሎት የሚሰጡ መጠጥ ቤቶችን ቁጥር ከ3 ሺህ እንዳይበልጥ የሚገድብ ህግ ልታወጣ መዘጋጀቷንና ይህ ህግ የሚጸድቅ ከሆነ በከተማዋ ከሚገኙት መጠጥ ቤቶች መካከል ከ75 በመቶ በላይ የሚሆኑት እንደሚዘጉኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
የከተማዋ የአልኮል መጠጦች ፈቃድ ቦርድ፣በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ያለውን የመጠጥ ሽያጭና ተጠቃሚነት ለመቀነስ በማሰብ የመጠጥ ቤቶችን ቁጥር የሚገድበውን ረቂቅ አዋጅ ባለፈው ሰኞ ለከተማዋ ምክር ቤት ማቅረቡን የጠቆመው ዘገባው፤ ከአምስት አመታት በፊት በከተማዋ ውስጥ ከነበሩት 200 መጠጥ ቤቶች መካከል ፈቃድ ያላቸው ሰባቱ ብቻ እንደነበሩም አስታውሷል፡፡
እ.ኤ.አ በ2016 የወጣ አንድ መረጃ በናይሮቢ ከተማ ውስጥ ከ12 ሺህ 500 በላይ መጠጥ ቤቶች እንደሚገኙና አብዛኞቹም ህገወጥ መሆናቸው መረጋገጡን ያስታወሰው ዘገባው፤ በከተማው በየሶስት ወሩ በአማካይ 50 አዳዲስ መጠጥ ቤቶች እንደሚከፈቱ አመልክቷል፡፡

Read 1206 times
Administrator

Latest from Administrator