Saturday, 06 April 2019 15:49

ደቡብ ኮርያ የ5ጂ ሞባይል ኔትወርክ በመጀመር ቀዳሚ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

አገልግሎቱን ለማግኘት የተመዘገቡት 5 ዝነኞች ብቻ ናቸው
 
           ደቡብ ኮርያ እጅግ ፈጣኑን የ5ጂ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት በማስጀመር በአለማችን ቀዳሚዋ አገር መሆኗን ዘ ቨርጅ ድረገጽ አስነብቧል፡፡
ኤስኬ ቴሌኮም የተባለውና በአገሪቱ ግዙፉ የዘርፉ ኩባንያ ትናንት በይፋ ያስጀመረውን እጅግ ፈጣን የ5ጂ ኔትወርክ ሞባይል ኔትወርክ በጥሩ ሁኔታ መጠቀም የሚችሉት ግን የጋላክሲ ኤስ10 ሞባይል ተጠቃሚዎች ናቸው ብሏል ዘገባው፡፡  
ፎርብስ መጽሄት በበኩሉ፤ ኩባንያው የጀመረው የ5ጂ የሞባይል ኔትወርክ አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን የተመዘገቡ ሰዎች አምስት የአገሪቱ ታዋቂ ሰዎች ብቻ እንደሆኑ ከትናንት በስቲያ ዘግቧል፡፡የዚህ ፈጣን የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ለመሆን ከተመዘገቡት አምስት ሰዎች መካከል ዩን ሱንግ ሂዩክ እና ኪም ዩና የተባሉት ደቡብ ኮርያውያን ዝነኛ ስፖርተኞች እንደሚገኙበትም ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 1080 times