በሰምና ወርቅ ኢንተርቴይንመንት በየወሩ የሚካሄደው “ሰምና ወርቅ” የኪነ ጥበብ ምሽት 16ኛው ዙር የፊታችን ረቡዕ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በቫምዳስ የመዝናኛ ማዕከል ይካሄዳል፡፡ በዕለቱም ዶ/ር አሉላ ፓንክረስት፣ ዶ/ር አዲል አብደላ፣ ዶ/ር ሙላቱ በላይነህ፣ ኮ/ል አትሌት ደራርቱ ቱሉ፣ አርቲስት ሀይሉ ፀጋዬ፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ፍሬው፣ መምህር ኤፍሬም ለማ፣ መምህርት ዕፀገነት ከበደ፣ የፊልም መምህር ኤሊያስ ማዳ፣ ገጣሚዎቹ ቴዎድሮስ ነጋሽና አስታውሽኝ ረጋሳ በመሶብ ባህላዊ ባንድ ታጅበው ዝግጅታቸውን እንደሚያቀርቡ አዘጋጁ ጋዜጠኛ ጌታቸው አለሙ አስታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና