Saturday, 23 March 2019 14:44

በአለማችን 2.1 ቢሊዮን ሰዎች ንጹህ ውሃ አያገኙም

Written by 
Rate this item
(3 votes)

35 በመቶ አፍሪካውያን የውሃ እጥረት ችግር ተጠቂ ናቸው

          በመላው አለም የሚገኙ 2.1 ቢሊዮን የተለያዩ አገራት ዜጎች አሁንም ድረስ ንጹህ የመጠጥ ውሃ እንደማያገኙ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል፡፡
ተመድ ባለፈው ማክሰኞ ይፋ ባደረገው አለማቀፍ የውሃ ልማት ሪፖርት እንዳለው፤ በአለማችን 4 ቢሊዮን ያህል ሰዎች ለከፋ የውሃ እጥረት ተጋልጠው ይገኛሉ፡፡ የከፋ የውሃ እጥረት ያለባቸው አገራት አብዛኞቹ በአፍሪካ እንደሚገኙና በአህጉሪቱ ከ35 በመቶ በላይ የሚሆነው ህዝብ የውሃ እጥረት ችግር ሰለባ እንደሆነ የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የአፍሪካ አገራት የህዝብ ቁጥር ከማደጉ ጋር በተያያዘ የውሃ ፍላጎት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ቢሆንም የውሃ አቅርቦትን ግን ለማሳደግ አለመቻሉን አመልክቷል፡፡
የአፍሪካ ልማት ባንክ ያወጣውን መረጃ ጠቅሶ ቢዝነስ ኢንሳይደር እንደዘገበው፣ በአፍሪካ አጠቃላይ የውሃና የስነ-ንጽህና አቅርቦትን ለማሟላት 66 ቢሊዮን ዶላር ያህል ገንዘብ እንደሚስፈልግ ይገመታል፡፡

Read 1301 times