Friday, 15 March 2019 00:00

ዚምባብዌ በሞባይል ኢንተርኔት ዋጋ ውድነት አለምን ትመራለች

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 አፍሪካዊቷ ዚምባቡዌ ከአለማችን አገራት መካከል ለሞባይል ኢንተርኔት እጅግ ውድ ዋጋ በማስከፈል ቀዳሚነቱን መያዟንና በአገሪቱ ለአንድ ጊጋ ባይት ኢንተርኔት 75.20 ዶላር እንደሚከፈል አንድ ጥናት አመልክቷል፡፡
ተቀማጭነቱ በእንግሊዝ የሆነው ኬብል የተባለ ተቋም፣ በ230 የአለማችን አገራት ውስጥ የሰራውን ጥናት መሰረት አድርጎ ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው መረጃ እንዳለው፣ ለአንድ ጊጋ ባይት የሞባይል ኢንተርኔት አገልግሎት ኢኳቶሪያል ጊኒ 65.83 ዶላር፣ ሴንት ሄለና 55.47 ዶላር፣ የፎክላንድ ደሴቶች 47.39 ዶላር፣ ጅቡቲ 37.92 ዶላር ዋጋ በማስከፈል በዋጋ ውድነት እስከ አምስተኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡
በአለማችን ለሞባይል ኢንተርኔት እጅግ በጣም አነስተኛውን ገንዘብ የምታስከፍለው ቀዳሚዋ አገር ህንድ መሆኗን የጠቆመው ተቋሙ፣ በአገሪቱ አንድ ጊጋ ባይት የሞባይል ኢንተርኔት 0.26 ዶላር ብቻ እንደሚያስከፍል አመልክቷል፡፡
ኬርጌዚስታን በ0.27 ዶላር፣ ካዛኪስታን በ0.49 ዶላር፣ ዩክሬን በ0.51 ዶላር፣ ሩዋንዳ በ0.56 ዶላር አንድ ጊጋ ባይት የሞባይል ኢንተርኔት በማቅረብ በዋጋ ርካሽነት እስከ አምስተኛ ደረጃ ይዘዋል ብሏል ጥናቱ፡፡ የሞባይል ኢንተርኔትን በርካሽ ዋጋ ከሚያቀርቡት ቀዳሚዎቹ 20 የአለማችን አገራት መካከል ግማሹ የእስያ አገራት መሆናቸውንም አክሎ ገልጧል፡፡

Read 4472 times