Print this page
Tuesday, 12 March 2019 00:00

የልብ ህመም በገዳይነት ቀዳሚው ነው ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)


        በአለማችን ሰዎችን በብዛት ለሞት በመዳረግ  የልብ ህመም ቀዳሚውን ስፍራ እንዲሚይዝና በፈረንጆች አመት 2017 ለሞት ከተዳረጉት 56 ሚሊዮን ሰዎች መካከል 32.3 በመቶ ያህሉን ለሞት የዳረጋቸውም የልብ ህመም መሆኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ አንድ አለማቀፍ ጥናትን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ ከልብ ህመም በመቀጠል በገዳይነት ሁለተኛ ደረጃን የያዘው ካንሰር ሲሆን፣ ጥናቱ በአመቱ ለሞት ከተዳረጉት ሰዎች መካከል 16.3 በመቶ ያህሉ በካንሰር ሰሰብ እንደሞቱም ገልጧል፡፡ የመተንፈሻ አካል በሽታዎች፣ ስኳር በሽታ እንደ ቅደም ተከተላቸው 6.5 በመቶ እና 5.8 በመቶ ያህሉን ሰዎች ለሞት የዳረጉ በሽታዎች መሆናቸውንም ጥናቱ አመልክቷል፡፡ በ2017 በርካታ ዜጎችን ለሞት ከዳረጉ ምክንያቶች መካከል አንዱ የመኪና አደጋ እንደነበር ያስታወሰው ጥናቱ፣ በአመቱ በመላው አለም 1.2 ሚሊዮን ያህል ሰዎችን ለሞት እንደዳረገም አስታውቋል፡፡

Read 1942 times
Administrator

Latest from Administrator