በሰምና ወርቅ ኢንቴርቴይንመንትና ኢቨንትስ አዘጋጅነት በየወሩ የሚካሄደው 15ኛው ዙር “ሰምናወርቅ” የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ የካቲት 28 ቀን 2011 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በቫምዳስ መዝናኛ ማዕከል ይካሄዳል፡፡በዕለቱ ዶ/ር ስርግው ገላው፣ ዶ/ር ዕሌኒ ገ/ መድህን፣ ወ/ሮ ሰሎሜ ታደሰ፣ ፀሐፊ ተውኔትና አዘጋጅ መዓዛ ወርቁ፣ መምህርት ዕፀገነት ከበደ፣ጋዜጠኛ ደግአረገ ነቃጥበብ፣ ተማሪ ዮናስ ዘውዴ ኮሜዲያን ምትኩ ፈንቴ፣ ገጣሚ የዓለምወርቅ አየለ እና ሌሎችም የጥበብ ሰዎች በመሶብ ባህላዊ ባንድ ታጅበው ስራቸውን እንደሚያቀርቡ አዘጋጆቹ ገልፀዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና