Print this page
Sunday, 03 March 2019 00:00

በኬንያ ፕሬዚዳንቱን መስሎ 100 ሺህ ዶላር ያጭበረበረው ተከሷል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ትራምፕንና ኪም ጆንግ ኡንን በመምሰል ያታለሉም ተይዘዋል

ከአነጋገርና አካሄዱ እስከ አለባበሱ መላ ሁኔታውን በመቀየር ራሱን ልክ እንደ ኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በማስመሰል፣ ከአንድ ባለሃብት 100 ሺህ ዶላር ያጭበረበረው ጄሴፍ ዋሳዋ የተባለ ኬንያዊ፣ ከሰባት ግብረ አበሮቹ ጋር ተይዞ ክስ እንደተመሰረተበት ተነግሯል፡፡
አጭበርባሪው ጆሴፍ ዋሳዋ ከግብረ አበሮቹ ጋር በመተባበር ራሱን ልክ እንደ ፕሬዚዳንቱ በማስመሰል በናይጀሪያ ስመ ጥር ለሆነ አንድ የመኪና ጎማ ኩባንያ ባለቤት በመደወል፣ መሬት ልሽጥልዎት የሚል ጥያቄ ማቅረቡን የጠቆመው ዘገባው፣ ድርድሩ በስልክ መጨረሱን አመልክቷል፡፡ የኩባንያው ባለቤት የደወለላቸው ፕሬዚዳንት ቡሃሪ ስለመሆኑ ቅንጣት ታህል ሳይጠራጠሩ ዋጋ መደራደራቸውንና የፋይናንስ ዳይሬክተራቸው ግዢውን እንዲጨርስና ክፍያውን እንዲፈጽም ማዘዛቸውን፣ ይህን ተከትሎም ሌሎች ተባባሪዎች፣ የፕሬዚዳንቱን የሚመስሉ ልዩ መኪኖችን ተከራይተው፣ ወደ ኩባንያው በመሄድ በተጭበረበረ ሰነድ ገንዘቡን መቀበላቸውን ገልጧል፡፡
በተያያዘ ዜና ደግሞ፣ መላ ነገሩ ቁርጥ የሰሜን ኮርያውን ኪም ጆንግ ኡንን የሚመስለው አውስትራሊያዊው ኮሜዲያን ሆዋርድ ኤክስ እና በሚገርም ሁኔታ ከትራምፕ ጋር የሚመሳሰለው ግብረ አበሩ፣ ባለፈው አርብ በቬትናም መዲና ሃኖኢ፣ ሁለቱን ፕሬዚዳንቶች መስለው፣ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሲሰጡ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተነግሯል፡፡
አጭበርባሪዎቹ ፕሬዚዳንቶች ትክክለኛዎቹ ኪምና ትራምፕ፣ በቬትናም ለመገናኘት የያዙትን ቀጠሮ እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም እነሱን መስለው፣ ህዝቡን ለመሸወድ ሲሞክሩ፣ እንደተነቃባቸውና ባለፈው ሰኞ ከአገር መባረራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡



Read 945 times
Administrator

Latest from Administrator