ባልተለመደ ሁኔታ እጅግና ከፍተኛ ሃይል ያለው ግዙፍ ባትሪ የተገጠመለትና ለ2 ተከታታይ ሰዓት ያህል ያለ ማቋረጥ ቪዲዮ ማጫወት የሚችል አዲስ ሞባይል ለእይታ መብቃቱ ተነግሯል፡፡ከሰሞኑ በባርሴሎና በተጀመረው አለማቀፍ የሞባይል አውደርዕይ ላይ ለእይታ የበቃውና በፈረንሳዩ የስልክ አምራች ኩባንያ አቬኒር ቴሌኮም የተመረተው ይህ የሞባይል ስልክ ፣ ከጎኑ ትልቅ ባትሪ የሚገጠምለትና 18 ሚሊሜትር ውፍረት ያለው ነው።
ፒ18ኬ ፖፕ የተባለው ይህ ሞባይል ስልክ የሚጠቀመው ባትሪ በግዝፈቱና በሃይሉ በአለማችን አቻ የሌለውና በአጭር ጊዜ ውስጥ ሙሉ ለሙሉ ቻርጅ መደረግ የሚችል ሲሆን፣ የሞባይል ስልኩ ለረጅም ሰዓታት ከማገልገሉ ውጭ ከሌሎች ስማርት ስልኮች የተለየ ነገር እንደሌለው ተነግሯል፡፡