Print this page
Monday, 04 February 2019 00:00

የኬንያው መሪ በ6 አመት 92 የውጭ አገራት ጉዞዎችን በማድረጋቸው ተተቹ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኬንያው ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ስድስት አመት ሊሞላው የ3 ወራት እድሜ በቀረው የስልጣን ዘመናቸው በድምሩ ለ92 ጊዜያት ያህል ወደ ውጭ አገራት መጓዛቸው፣ በአገሪቱ ተቃዋሚዎች ዘንድ መተቸቱን ኦል አፍሪካን ኒውስ ዘግቧል፡፡
በሚያዝያ 2013 ወደ ስልጣን የመጡት ኡሁሩ፤ በስልጣን ዘመናቸው ወደ ውጭ አገራት ካደረጓቸው 92 ጉዞዎች መካከል አብዛኞቹ ያን ያህል ጥቅም የሌላቸው ናቸው በሚል የሚተቹ ቢኖሩም፣ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ግን ፕሬዚዳንቱ ያደረጓቸው ጉዞዎች ዲፕሎማሲን በማጠናከርና አገሪቱ በአለማቀፍ መድረክ ያላትን ቦታ ከፍ በማድረግ ረገድ ቁልፍ ሚና የተጫወቱ ናቸው ሲል አስተባብሏል፡፡  
አንዳንድ የአገሪቱ ተቃዋሚዎችና የፖለቲካ ተንታኞች በበኩላቸው፤በተለይ ከፕሬዚዳንቱ ጋር የሚጓዙ ልዑካን በርካታ ቁጥር ያላቸው ከመሆናቸው ጋር በተያያዘ አገሪቱን ላላስፈላጊ ወጭ ዳርጓታል በሚል ትችታቸውን እንደሰነዘሩ ዘገባው አስነብቧል፡፡ ኡሁሩ ኬንያታ ባለፉት ስድስት አመታት ውስጥ ወደ ውጭ አገራት ያደረጉት ጉዞ፣ ከቀድሞው የአገሪቱ መሪ ሙዋይ ኪባኪ በ3 እጥፍ ያህል እንደሚበልጥ የጠቆመው ዘገባው፤ ኪባኪ በ10 አመታት የስልጣን ዘመናቸው ወደ ውጭ አገራት የተጓዙት 33 ጊዜ ያህል ብቻ መሆኑን አስታውሷል፡፡
ኡሁሩ አብዛኛዎቹን ጉዞዎች ያደረጉት ወደተለያዩ የአፍሪካ አገራት ቢሆንም፣ ወደ አውሮፓ ለ12፣ ወደ አሜሪካ ለ4፣ ወደ ቻይና ለ4፣ ወደ ህንድ ለ2 እንዲሁም ወደ ሌሎች የአለም አገራት አንድ አንድ ጊዜ ያህል መጓዛቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡

Read 2057 times
Administrator

Latest from Administrator