Print this page
Monday, 28 January 2019 00:00

ጠ/ሚ ዐቢይ “ከአመቱ ምርጥ አለማቀፍ አሳቢዎች” አንዱ ሆነዋል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የአሜሪካው ታዋቂ መጽሄት ፎሪን ፖሊሲ፤ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድን ከአለማችን የአመቱ 100 ምርጥ አለማቀፍ አሳቢዎች አንዱ አድርጎ መርጧቸዋል፡፡
መጽሄቱ ከሰሞኑ ይፋ ባደረገው የ2019 የፈረንጆች አመት 100 ምርጥ አለማቀፍ አሳቢዎች ዝርዝር ውስጥ ባሰፈረው ጽሁፍ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አንድ አመት ባልሞላው የስልጣን ዘመናቸው፣ ከጎረቤት አገር ኤርትራ ጋር ሰላም በመፍጠር ታሪክ ሰርተዋል፤ በሁለቱ አገራት መካከል ሰላም መስፈኑ የተለያዩ ቤተሰቦችን ከማገናኘት ባለፈ በአገራቱ መካከል ለረጅም ጊዜያት ተቋርጦ የነበረውን የንግድ ግንኙነት እንዲቀጥል በር ከፍቷል ብሏል፡፡
መከላከያና ደህንነት በሚለው መስክ በምርጥ አለማቀፍ አሳቢነት ያካተታቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ በአሁኑ ወቅት በአገር ውስጥ ያሉ ልዩነቶችን በመፍታት ላይ ትኩረት አድርገው እየሰሩ እንደሚገኙም ጠቁሟል፡፡
ፎሪን ፖሊሲ መጽሄት ለአስረኛ ጊዜ ባወጣው አመታዊው የ100 ምርጥ አለማቀፍ አሳቢዎች ዝርዝር ውስጥ በፖለቲካ፣ በደህንነት፣ በቴክኖሎጂ፣ ኢኮኖሚ፣ ንግድ፣ ሳይንስ፣ ጤናና ሌሎች መስኮች ተጽዕኖ የፈጠሩ አለማቀፍ አሳቢዎችን በ10 የተለያዩ ዘርፎች ነው ግለሰቦችን ያካተተው፡፡
በዘንድሮው የመጽሄቱ ዝርዝር ውስጥ ከተካተቱት መካከልም የአይኤምኤፍ ዳይሬክተር ክርሲያን ላጋርድ፣ የጀርመኗ መራሂተ መንግስት አንጌላ መርኬል፣ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ፣ የአማዞን መስራች ጄፍ ቤዞስና የደቡብ ኮርያ ፕሬዚዳንት ሙን ጃኢን ይገኙበታል፡፡

Read 1509 times
Administrator

Latest from Administrator