Saturday, 19 January 2019 00:00

ከተመድ ሰራተኞች 33% ያህሉ ወሲባዊ ትንኮሳ ተፈጽሞባቸዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በተባበሩት መንግስታት ድርጅት ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ተቋማት ተቀጥረው ከሚሰሩ ሰራተኞች መካከል 33 በመቶ ያህሉ ባለፉት 2 አመታት የተለያዩ አይነት የወሲባዊ ትንኮሳ ድርጊቶች እንደተፈጸሙባቸው የሚያሳይ አዲስ የጥናት ውጤት ይፋ መደረጉን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
ባለፈው ማክሰኞ ይፋ የተደረገውንና ከ30 ሺህ በላይ በሚሆኑ የተመድ ሰራተኞች ላይ የተሰራውን አዲስ የጥናት ውጤት ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፤ በርካታ የተመድ ሰራተኞች በቢሯቸውና በመስክ ስራቸውን በማከናወን ላይ እያሉ የስራ ባልደረቦችና አለቆችን ጨምሮ በተለያዩ ግለሰቦች ወሲባዊ ትንኮሳዎች እንደተደረጉባቸው ተናግረዋል፡፡
በሰራተኞቹ ላይ ወሲባዊ ትንኮሳ ፈጽመዋል ከተባሉት ሰዎች መካከል 60 በመቶ ያህሉ ወንዶች መሆናቸውን የጠቆመው ዘገባው፤ ትንኮሳ ከተፈጸመባቸው መካከል በተንኳሾች ላይ እርምጃ የወሰዱት ደግሞ 30 በመቶው ያህል ብቻ ናቸው መባሉን አመልክቷል፡፡

Read 1011 times