Print this page
Saturday, 12 January 2019 14:53

ኤሚኔም በአመቱ የአልበም ሽያጭ ቀዳሚነቱን ይዟል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የኦባማ ነጠላ ዜማ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፏል


    በተጠናቀቀው የፈረንጆች አመት 2018 ከፍተኛ የሙዚቃ አልበም ሽያጭ ያስመዘገቡ የአለማችን ምርጥ ድምጻውያን ዝርዝር ይፋ የተደረገ ሲሆን፣ ካናዳዊው ራፐር ኤሚኔም በአመቱ 755 ሺህ 27 አልበሞችን በመሸጥ የአንደኛ ደረጃን መያዙ ተነግሯል፡፡
በዝአንግል የተባለው ድረገጽ ባወጣው አለማቀፍ የሙዚቃ አልበሞች ሽያጭ ደረጃ መሪነቱን የያዘው የ46 አመቱ ራፐር ኤሚኔም፤ በተለይም በቅርቡ ያወጣው ካሚካዚ የተሰኘ አስረኛው አልበሙ 373 ሺህ 67 ኮፒ እንደተሸጠለት አመልክቷል፡፡ ድረገጹ ባወጣው መረጃ እንዳለው፤ በአመቱ የአልበም ሽያጭ የሁለተኛ ደረጃን የያዘው ቢቲኤስ የተባለው የሙዚቃ ቡድን ሲሆን፣ 603 ሺህ 307 አልበሞች ተሸጦለታል፡፡
በሌላ በኩል፤የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማ የለቀቁት ዋን ላስት ታይም የተሰኘ ነጠላ ዜማ ከፍተኛ ተወዳጅነትን ማትረፉንና በቢልቦርድ የአርኤንድ ቢ ሙዚቃ የደረጃ ሰንጠረዥ 22ኛ ደረጃን መያዙን ፎርብስ ዘግቧል፡፡
ኦባማ ከክርስቶፈር ጃክሰንና ቢቢ ዊናንስ ከተባሉ ድምጻውያን ጋር በጋራ የሰሩትና እንደገና በአዲስ መልክ ተሰርቶ በቅርቡ የወጣው ይህ ነጠላ ዜማ በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ብቻ 9 ሺህ ጊዜ ያህል ዳውንሎድ የተደረገ ሲሆን፣ በድረገጽ አማካይነትም ከ307 ሺህ ጊዜ በላይ በቀጥታ መታየቱ ተነግሯል፡፡

Read 1427 times
Administrator

Latest from Administrator