Tuesday, 01 January 2019 00:00

የስደተኞች ቁጥር

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በ2018 የስደተኞች ቁጥር በአለማቀፍ ደረጃ በከፍተኛ ሁኔታ ያደገ ሲሆን 6.3 ሚሊዮን ያህል ዜጎቿ የተሰደዱባት ሶርያ በአለማችን እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ዜጎች አገራቸውን ጥለው የተሰደዱባት ቀዳሚዋ አገር መሆኗን ዩኤስኤ ቱዴይ ዘግቧል፡፡
ከአለማችን አገራት በርካታ ዜጎችን በማሰደድ የሁለተኛ ደረጃን የያዘቺው 2.6 ሚሊዮን ያህል ዜጎች የተሰደዱባት አፍጋኒስታን ናት ያለው ዘገባው፣  እ.ኤ.አ በ2011 ነጻነቷን ያወጀቺውና እንደ አገር መቆም ተስኗት በእርስ በእርስ ጦርነት ስትታመስ የኖረቺዋ ደቡብ ሱዳን በ2.4 ሚሊዮን ስደተኞች የሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧንም አመልክቷል፡፡
ሌላዋ አፍሪካዊት አገር ሶማሊያ በ806 ሺህ ያህል ስደተኞች የአራተኛ ደረጃን ይዛለች ያለው ዘገባው፣ 723 ሺህ ያህል የሮሂንጋ ሙስሊሞች ወደ ጎረቤት አገር ባንግላዴሽ የተሰደዱባት ማይንማር በአምስተኛ ደረጃ ላይ እንደምትገኝ አመልክቷል፡፡

Read 838 times