Tuesday, 01 January 2019 00:00

ትኩረት የሳቡ አነጋጋሪ ጉዳዮች

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በአመቱ በአለማችን ከተከሰቱ አነጋጋሪና የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስበው ከከረሙ ጉልህ አለማቀፋዊ ጉዳዮች መካከል በቱርክ የሳዑዲ አረቢያ ኢምባሲ የተፈጸመው የጋዜጠኛ ጀማል ካሾጊ ግድያ ይጠቀሳል፡፡
ቻይናና አሜሪካ የገቡበትና ዳፋው ለበርካታ የአለም አገራት ይተርፋል ተብሎ የተሰጋው የንግድ ጦርነት፣ አሜሪካ ከኢራን ጋር የገባቺውን የኒውክሌር ስምምነት በማፍረስ ተጨማሪ ማዕቀብ መጣሏና ለኢየሩሳሌም የእስራኤል መዲናነት በይፋ እውቅና መስጠቷ፣ በውዝግብ የታጀበው የእንግሊዝ ከአውሮፓ ህብረት የመውጣት ዕቅድም በአመቱ አለማቀፋዊ ትኩረትን ስበው የከረሙ ጉዳዮች ናቸው፡፡
ተካርረው የከረሙትና ከዛሬ ነገ ወደ ኒውክሌር ጦርነት ይገባሉ ተብሎ አለም በስጋት ይመለከታቸው የነበሩት ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕና የሰሜን ኮርያው አቻቸው ኪም ጆንግ ኡን ባልተጠበቀ መልኩ አቋማቸውን ቀይረው በወርሃ ሰኔ ሲንጋፖር ውስጥ ታሪካዊውን ሰላማዊ ውይይት ማድረጋቸውና ኪም ኒውክሌራቸውን ሊያወድሙ መስማማታቸው የአለምን ትኩረት የሳበ ሌላው ጉዳይ ነበር፡፡
የኮንጎ የኢቦላ ወረርሽኝ፣ የሩስያው የአለም የእግር ኳስ ዋንጫ፣ የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት፣ የሳኡዲ አረቢያው ልኡል ሞሀመድ ቢን ሳልማን ሚኒስትሮችንና ባለሃብቶችን በሙስና ሰበብ ድንገት ማሰራቸው፣ የፈረንሳይ ተቃውሞና የዚምባቡዌው ሙጋቤና የደቡብ አፍሪካው ጃኮብ ዙማ ከመንበረ ስልጣን መወገድም በ2018 የመገናኛ ብዙሃንን ትኩረት ስበው ከከረሙ አለማቀፋዊ ጉዳዮች ተርታ ይሰለፋሉ፡፡


---------------

Read 1194 times