Wednesday, 02 January 2019 00:00

“የሕዳሴው መሐንዲስ” መጽሐፍ በገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  በ”አዲስ አድማስ” ጋዜጣ በተለያዩ ርዕስ ጉዳዮች ላይ መጣጥፎችን፣ ወጎችንና አጫጭር ልብወለዶችን በመጻፍ የሚታወቀው ደረጀ ይመር ያዘጋጀው “የሕዳሴው መሐንዲስ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል፡፡
መጽሐፉ፤ እውነተኛው የሕዳሴው መሐንዲስ ታላቁ የኢትዮጵያ ንጉሥ አጼ ቴዎድሮስ እንደሆኑ የሚያትት መጣጥፍን ጨምሮ ሌሎች ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ፍልስፍናዊ ይዘቶችን የሚዳስሱ ጽሁፎች፣አዝናኝ ወጎችና አጫጭር ልብወለዶችን አካትቶ ይዟል። በ30 ምዕራፎች ተከፍሎ በ202 ገጾች የተቀነበበው መጽሐፉ፤ በ150 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ መጽሐፉን ጃፋር መጻሕፍት መደብር እንደሚያከፋፍለው ታውቋል፡፡   

Read 3797 times