Saturday, 19 May 2012 12:41

ሊፋን አዲሱ መኪናውን ዛሬ ያስመርቃል

Written by  ግሩም ሠይፉ
Rate this item
(3 votes)

 

ሊፋን ሞተርስ ኩባንያ” “ሊፋን X-60” የተሰኘችውን አዲስ አውቶሞቢል ዛሬ በአዲሱ  የአፍሪካ ህብረት ህንጻ በሚደረግ የእራት ግብዣ ለኢትዮጵያ ገበያ በይፋ እንደሚያቀርብ አስታወቀ፡፡ለኩባንያው ሰባተኛ ምርት የሆነችው “ሊፋን X-60 ኤግዚኪዩቲቭ” አውቶሞቢል ለከተማ ጐዳናዎች ምቹ መሆኗን የተናገሩት የኩባንያው ኃላፊ” የመኪናዋ ዋጋ 530ሺ ብር እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ኩባንያው የመጀመሪያዋን መኪና የ“እግር ኳስን በሬዲዮ ተመልከቱ” አዘጋጅ ለሆነው መሰለ መንግስቱ በዛሬው ዕለት በሚካሄደው የምርቃት ስነስርዓት ላይ እንደሚሸልም ታውቁዋል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት “ሊፋን - 520” አውቶሞቢል ከዚሁ ኩባንያ የተሸለመው ኮሜንታተር መሰለ መንግስቱ” መኪናዋን 21ሺ ኪሎሜትር እንደነዳትና በደህና ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ለአዲስ አድማስ ገልፆዋል፡፡

የሊፋን ልዩ አምባሳደር በመሆን አዲሱዋን “ሊፋን X-60” መሸለሙን በተመለከተ ተጠይቆ በሰጠው ምላሽ “ለሽልማቱ ያበቃኝ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጫፍ ጫፍ የሰጠኝ ፍቅር ነው ለተደራራቢ ድሎች ያበቃኝ” መላው ህዝብ ይመስገንልኝ” ብሏል-ኮሜንታተር መሰለ፡፡ሊፋን ሞተርስ “ሪካርዶ” ከተባለው የብሪቲሽ ሞተር አምራች ኩባንያ ጋር በመተባበር  ቪቪ ቲ አይ የተባለ የስፖርት መኪና ሞተር ለአዲሱዋ አውቶሞቢል እንደተገጠመላት የገለፁት የኩባንያው ሃላፊ “ሞተሩ መኪናዋ በአነስተኛ ነዳጅ ከፍተኛ ጉልበት እንዲኖራት የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡ ለኩባንያው በቀረበ ትዕዛዝ መሰረት” በመጪው ሁለት ወር ውስጥ 40 ሊፋን መኪናዎች ወደ አገር ውስጥ እንደሚገቡ ተገልፅዋል፡፡ እስካሁን በኢትዮጵያ ከ3ሺ በላይ የሊፋን ምርት የሆኑ መኪኖች መሸጣቸውን የገለፁት የኩባንያው ኃላፊ” መኪኖቹ በትዕዛዝ ቶሎ ግዢያቸው ሊፈፀም መቻሉ ተፈላጊ እንዳደረጋቸው ተናግረዋል፡፡

 

 

 

 

 

Read 20417 times Last modified on Saturday, 19 May 2012 12:44