Print this page
Tuesday, 11 December 2018 00:00

የሁዋዌ ባለስልጣኗ እስር የአሜሪካንና ቻይናን ፍጥጫ ያባብሰዋል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በአለማችን ሁለተኛው ግዙፍ የስማርት ፎን አምራች ኩባንያ የሆነው የቻይናው ሁዋዌ የፋይናንስ ዋና ሃላፊ ዋንዙ ሜንግ ባለፈው ረቡዕ በአሜሪካ ባለስልጣናት ጥያቄ በካናዳ መታሰራቸውን ተከትሎ ጉዳዩ ሁለቱን አገራት ወደከፋ ነገር ሊያመራቸው እንደሚችል እየተነገረ ነው፡፡
የካናዳ መንግስት አሜሪካ በኢራን ላይ የጣለችውን የንግድ ማዕቀብ ጥሰዋል በሚል በቁጥጥር ስር የዋሉትን ዋንዙ ሜንግ ለአሜሪካ አሳልፎ እንደሚሰጥ እየተገለጸሲሆን ጉዳዩ ከሰሞኑ የመርገብ አዝማሚያ የታየበትንና ለወራት የዘለቀውን የአሜሪካና የቻይና የንግድ ጦርነት ዳግም ሊቀሰቅሰውና በአገራቱ መካከል የባሰ ፍጥጫን ሊያስከትል እንደሚችል መነገሩን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
በካናዳ የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ፣ የካናዳ መንግስት ግለሰቧን ማሰሩን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ነው ሲል ያወገዘው ሲሆን ለአሜሪካ አሳልፎ የመስጠት ሃሳቡን በመሰረዝ በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቅቃቸውም ጠይቋል፡፡
ለወራት በንግድ ጦርነት ውስጥ የዘለቁት አሜሪካና ቻይና ከሰሞኑ ግን በጉዳዩ ዙሪያ መክረው መግባባት ላይ እስከሚደርሱ ድረስ ለሶስት ወራት ያህል አንዳቸው በሌላኛቸው ምርቶች ላይ ቀረጥ ላለመጣል መስማማታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡

Read 2337 times
Administrator

Latest from Administrator