Print this page
Monday, 10 December 2018 00:00

በቬንዙዌላ የአንድ ሲኒ ቡና ዋጋ በ286 ሺህ% ጨምሯል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የተዛባ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ባስከተለው የዋጋ ግሽበትና የኑሮ ውድነት ዜጎች የከፋ ኑሮን በሚገፉባት ቬንዙዌላ፤ የአንድ ሲኒ ቡና ዋጋ ባለፉት 12 ወራት ጊዜ ውስጥ በ286 ሺ % ጭማሪ ማሳየቱን ብሉምበርግ ዘግቧል፡፡
መላው የጠፋቸው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ኒኮላስ ማዱሮ ከሰሞኑ ለሰራተኞች በአመቱ ስድስተኛው የደመወዝ ጭማሪ የሆነውን የ150 በመቶ የደመወዝ ጭማሪ ማድረጋቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ ይህን ተከትሎም ዜጎች ሸቀጦችን ለመግዛት ወረፋ ይዘው መዋል ማደር መጀመራቸውንና የዋጋ ግሽበትም በከፍተኛ ሁኔታ በመጨመር ላይ እንደሚገኝ አመልክቷል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ገንዘብ በገፍ እያተመ ማሰራጨቱ የዋጋ ግሽበቱን እየጨመረው እንደሚገኝ የተነገረ ሲሆን፣ የደመወዝ ጭማሪው መደረጉን ተከትሎ በመዲናዋ ካራካስ የአንድ ሲኒ ቡና ዋጋ ከእጥፍ በላይ መጨመሩን፣ የበርገር ዋጋም ባለፈው ሳምንት በ52 በመቶ ያህል መጨመሩን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡
በሌላ ዜና ደግሞ ላይቤሪያ በአስከፊ የኤሌክትሪክ ሃይል አቅርቦት እጥረት ውስጥ መዘፈቋንና ለቀውሱ በምክንያትነት ከሚጠቀሱት ጉዳዮች ዋነኛው አገሪቱ ከምታመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ውስጥ 60 በመቶ ያህል በዜጎች የሚዘረፍ መሆኑ ነው ሲል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በላይቤሪያ በየአመቱ ከሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ውስጥ 60 በመቶ ያህሉን ዜጎች ህገወጥ በሆነ መልኩ በስውር መስመር በመቀጠል ለቤታቸውና ለድርጅታቸው እያስገቡ በነጻ እንደሚጠቀሙበት የአገሪቱ የኤሌክትሪክ ኮርፖሬሽን ማስታወቁን ዘገባው ገልጧል፡፡
አገሪቱ በህገወጥ መንገድ በዜጎች በምትዘረፈው ከፍተኛ መጠን ያለው የኤሌክትሪክ ሃይል በየአመቱ 35 ሚሊዮን ዶላር ያህል እንደምታጣ ያስታወቀው ኮርፖሬሽኑ፣ በዚህ ህገወጥ ድርጊት ላይ የተሰማሩትን ዜጎች በቁጥጥር ስር ለማዋል ብሄራዊ ግብረሃይል ተቋቁሞ ዘመቻ መጀመሩንም አመልክቷል፡፡

Read 1184 times
Administrator

Latest from Administrator