Sunday, 02 December 2018 00:00

የሌሴቶ ፓርላማ አባላት ደመወዛቸውን በእጥፍ ሊያስጨምሩ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 የህዝብ ብዛት ፈተና በሆነባትና ኢኮኖሚያዋ በማያወላዳው ሌሴቶ፤ ከፍተኛ ተከፋይ ከሆኑ ዜጎች መካከል የሚጠቀሱት የአገሪቱ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ደመወዛቸው በእጥፍ እንዲጨመርላቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡የስራ አጥነት ችግር 39 በመቶ ያህል በደረሰባት ሌሴቶ፣የፓርላማ አባላቱ የደመወዝ ጭማሬ እንዲደረግላቸው ጥያቄ ማቅረባቸውን ተከትሎ፣ የአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶማስ ታባኔ፣ ለፋይናንስ ሚኒስትሩ፣ የደመወዝ ማስተካከያ ዕቅድ እንዲያወጡና እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ መስጠታቸውንም ዘገባው አመልክቷል።
የፓርላማ አባላቱ ያቀረቡት እጥፍ የደመወዝ ጭማሪ ተቀባይነት የሚያገኝ ከሆነ፣ አንድ የሌሴቶ ፓርላማ አባል በወር 5 ሺህ 344 ዶላር ያህል ደመወዝ እንደሚበላ የጠቆመው ሪፖርቱ፤ በአገሪቱ መደበኛ የመንግስት ሰራተኞች የሚያገኙት ወርሃዊ ደመወዝ በአማካይ 144 ዶላር ብቻ እንደሆነም ገልጧል፡፡
75 በመቶ ያህሉ ህዝቧ በገጠር እንደሚኖርና ኑሮውን በግብርና ላይ መሰረት ያደረገ እንደሆነ የገለጸው ዘገባው፤ ግማሽ ያህሉ የአገሪቱ ቤተሰብ ኑሮውን የሚመራውም፣ በደቡብ አፍሪካ፣ የስደት ኑሮን የሚገፋ ወዳጅ ዘመዱ በሚልክለት የድጎማ ገንዘብ እንደሆነ አክሎ አስረድቷል፡፡


Read 2986 times