በነገው የቢልቦርድ ሚዩዚክ አዋርድ ለሁለተኛ ጊዜ “አይኮን አዋርድ” ተብሎ የሚሰጠውን የክብር ሽልማት ስቲቪ ወንደር እንደሚሸለምም ታውቋል፡፡ በ2012 የቢልቦርድ ሙዚቃ አዋርድ ላይ በፍፃሜ ተፋላሚነት በብዙ ዘርፎች በመታጨት “የአመቱ ምርጥ አርቲስት” እና “የዓመቱ ምርጥ ሴት አርቲስት”ን ጨምሮ በ18 ዘርፎች የታጨችው እንግሊዛዊቷ አዴሌ እና በ17 የሽልማት ዘርፎች የታጨው የኤሌክትሮ ፖፕ ሙዚቃ ቡድን ኤልኤምኤፍኤኦ ይመራሉ፡፡ ባለፈው ዓመት በከፍተኛ ዘርፎች ታጭታ ግንባር ቀደም የነበረችው ሪሃና በ13 የሽልማት ዘርፎች ስትከተል፤ ሌዲ ጋጋ እና ሊል ዋይኔ በእኩል 10 የሽልማት ዘርፎች እጩ ሆነው ቀርበዋል፡፡ የዓመቱ ምርጥ ሴት አርቲስት በሚለው የውድድር ዘርፍ ፉክክሩ በአዴሌና ሪሃና መካከል ሲሆን በዓመቱ ምርጥ አዲስ አርቲስት ደግሞ ኬቲ ፔሪና ዊዝ ካሊፋ ይፎካከራሉ ተብሏል፡፡ አርቲስቶቹ በዓመቱ ምርጥ አርቲስት ሽልማት ከፍተኛ ፉክክር ላይ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡ አምና የዓመቱ ምርጥ አርቲስት ተብሎ ከፍተኛውን ሽልማት የወሰደው ራፕሩ ኤሚነም ነበር፡፡