ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን ፋሽኑ ካለፈበትና ባለቀለም ቴሌቪዥን ከመጣ ከ50 አመታት በላይ ቢሆነውም፣ በእንግሊዝ ከ7 ሺህ በላይ ቤተሰቦች አሁንም ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን እንደሚያዩ ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
በእንግሊዝ ባለቀለም ቴሌቪዥን ገበያ ላይ የዋለው እ.ኤ.አ በ1967 እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፣ በአገሪቱ 7 ሺህ 161 ያህል ቤተሰቦች አሁንም ድረስ ቴሌቪዥናቸውን እንዳልቀየሩ አመልክቷል፡፡ ባለቀለም ቴሌቪዥን ከመጣ በኋላ ጥቁርና ነጭ ቴሌቪዥን የሚገዙ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ቢሆንም አንዳንዶች ግን ለመቀየር አለመፈለጋቸውን ዘገባው አስረድቷል፡፡