Saturday, 10 November 2018 13:28

ዘንድሮ በሜዲትራኒያን ከ2ሺህ በላይ ስደተኞች ለሞት ተዳርገዋል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

 በፈረንጆች አመት 2018 ያለፉት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ሜዲትራኒያን ባህርን አቋርጠው ወደ አውሮፓ ለመግባት በጉዞ ላይ ሳሉ በባህር ውስጥ ሰጥመው የሞቱ የተለያዩ አገራት ስደተኞች ቁጥር፣ ከ2ሺህ በላይ መሆኑን ተመድ አስታውቋል፡፡የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ተቋም ያወጣው ሪፖርት እንደሚለው፤ በሜዲትራኒያን ባህር በአስቸጋሪ ጉዞ ውስጥ አልፈው ወደ አውሮፓ ለመግባት ሲሞክሩ ለተለያዩ አሰቃቂ አደጋዎችና ለሞት የሚዳረጉ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ ይገኛል፡፡
ህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ስደተኞችን በአደገኛ ሁኔታ ውስጥ ማጓጓዛቸው መበራከቱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ አደጋዎች በሚከሰቱበት ጊዜ ፈጥነው የሚደርሱና የነፍስ አድን ስራ የሚሰሩ መንግስታዊ ያልሆኑና አለማቀፍ ተቋማት ስራቸውን እንዳይሰሩ መታገዳቸው ለሟቾች ቁጥር መጨመር አንዱ ምክንያት መሆኑንም አመልክቷል፡፡

Read 1409 times