በአገሪቱ ከ88 ሚሊዮን በላይ ዜጎች በከፋ ድህነት ውስጥ ይገኛሉ
ባለፉት አራት ወራት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ናይጀሪያውያን ወደ ከፋ ድህነት መግባታቸውንና በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ቁጥር 88 ሚሊዮን መድረሱን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
ተቀማጭነቱን በቪየና ያደረገው ወርልድ ፖቨርቲ ክሎክ የተሰኘ ተቋም ይፋ ባደረገው አለማቀፍ ሪፖርት እንዳለው፣ ከ1.9 ዶላር በታች ዕለታዊ ገቢ ባላቸው ወይም በከፋ ድህነት ውስጥ በሚገኙ ዜጎች ብዛት ናይጀሪያ ከአለማችን አገራት በቀዳሚነት ትገኛለች፡፡
በናይጀሪያ ድህነት ስር እየሰደደ እንደሚገኝ የጠቆመው ተቋሙ፣ መንግስት ችግሮችን ለመፍታት እያደረገ ያለው ጥረት በቂ አለመሆኑንና አገሪቱ በ2030 ከድህነት ለመውጣት ያስቀመጠችውን ግብ ለማሳካት እንደማትችል የሚያመላክቱ ሁኔታዎች መኖራቸውንም አስረድቷል፡፡ የቢልና ሚሊንዳ ጌትስ ፋውንዴሽን ያወጣውን ትንበያ ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በመጪዎቹ 12 አመታት ጊዜ ውስጥ ከአለማችን እጅግ ድሃ ሰዎች መካከል ከ40 በመቶ በላይ የሚሆኑት በናይጀሪያ እንደሚገኙ ይጠበቃል፡፡
የአለም ባንክ በበኩሉ፤ በመላው አለም በከፋ ድህነት ውስጥ የሚገኙ ሰዎች ቁጥር ከ1.6 ቢሊዮን በላይ መድረሱን ያስታወቀ ሲሆን፣ ከ29 በመቶ በላይ የሚሆኑትም ከሰሃራ በታች በሚገኙ አገራት እንደሚኖሩ አስረድቷል፡፡
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል