ሚዩዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በአርክቴክት ሚካኤል ሽፈራው “የማስጠንቀቂያ ደወል” መፅሐፍ
ላይ በብሔራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የገቨርናንስና ዴቨሎፕመንት
ትምህርት ክፍል መምህር ሲሆኑ መድረኩን የሚመሩት አቶ ሰለሞን ተሰማ ጂ ናቸው ተብሏል።ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Saturday, 27 October 2018 10:43
“የማስጠንቀቂያ ደወል” ላይ ነገ ውይይት ይካሄዳል
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና