Print this page
Sunday, 28 October 2018 00:00

2.3 ቢሊዮን ሰዎች በዋጋ ውድነት የተነሳ ኢንተርኔት አይጠቀሙም

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


በመላው አለም በሚገኙ የተለያዩ አገራት የኢንተርኔት ዋጋ ከአቅማቸው በላይ በመሆኑ ሳቢያ አገልግሎቱን መጠቀም ያልቻሉ ሰዎች ቁጥር ከ2.3 ቢሊዮን በላይ መድረሱን አንድ አለማቀፍ የጥናት ሪፖርት አስታውቋል፡፡
አሊያንስ ፎር አፎርዴብል ኢንተርኔት የተባለው ተቋም በ61 የአለማችን አገራት ላይ የሰራውን ጥናት መሰረት አድርጎ ሰሞኑን ይፋ ባደረገው አመታዊ ሪፖርቱ እንዳለው፣ ጥናቱ ከተሰራባቸው አገራት መካከል ከ60 በመቶ በላይ የሚሆኑት ከዜጎች የመክፈል አቅም በላይ የሆነ የኢንተርኔት ዋጋ ተመን ያላቸው ናቸው፡፡
በሁሉም አገራት የአንድ ጊጋ ባይት ኢንተርኔት ክፍያ ዋጋ ከአገራቱ አማካይ ወርሃዊ ገቢ ከ5 በመቶ በላይ እንደሚደርስ የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የኢንተርኔት አገልግሎት ክፍያ ውድነት በርካታ ዜጎችን የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ከፍተኛ እንቅፋት መሆኑን ቀጥሏል፡፡ በአለማችን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር እድገት በአመቱ ቅናሽ ማሳየቱን የጠቆመው ሪፖርቱ፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በ2017 መጨረሻ ላይ የአለማችንን የኢንተርኔት አቅርቦት 50 በመቶ ለማድረስ ያስቀመጠውን ግብ ማሳካት እንዳልተቻለም አመልክቷል፡፡

Read 2302 times
Administrator

Latest from Administrator