Print this page
Sunday, 21 October 2018 00:00

በላይቤሪያ ዊግና የጸጉር ቀለም የሚጠቀሙ ሰራተኞች ሊቀጡ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 የላይቤሪያ የገንዘብ ሚኒስቴር፤ ጸጉራቸውን ቀለም የሚቀቡና ተፈጥሮ የለገሰቻቸውን ጸጉር ለማስረዘም ሲሉ ሰው ሰራሽ ጸጉር ወይም ዊግ የሚቀጥሉ ሴት ሰራተኞቹን እንደሚቀጣ ማስታወቁን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በአገሪቱ የመንግስት ሰራተኛ የሆኑ ሴቶች ጸጉራቸውን እንዳያቀልሙና ዊግ እንዳይጠቀሙ የሚከለክል ህግ ከወጣ አራት አመታት ያህል ቢሆነውም፣ የመንግስት ተቋማት ህጉን ተግባራዊ ሳያደርጉት እንደቆዩ ያስታወሰው ዘገባው፤ የገንዘብ ሚኒስቴር ግን ከሰሞኑ ድርጊቱን በሚፈጽሙ ሰራተኞቹ ላይ ቅጣት እንደሚጥል ማሳሰቡን አመልክቷል፡፡
ሚኒስቴሩ ሰራተኞቹን ማስጠንቀቁን ተከትሎ በርካታ የአገሪቱ ዜጎች በማህበራዊ ድረገጾችና በተለያዩ አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ተቃውሟቸውን ያሰሙ ሲሆን ህጉን ከአባታዊ ባህል የመነጨ አግባብነት የሌለው ጾታዊ መድልዖ ሲሉ መተቸታቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡ ሴቶች  ቀለም መቀባታቸውም ሆነ ዊግ ማድረጋቸው በስራ ገበታቸው በሚያስመዘግቡት ውጤት ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተጽዕኖ የለውም፣ ምንም አይነት መሰረት የሌለው ያልተገባ ክልከላ ነው ሲሉም ተቃውሟቸውን ሰንዝረዋል፡፡
የመንግስት ሰራተኛ የሆኑ ላይቤሪያውያን ሴቶችን የጸጉር ቀለምና ዊግ አጠቃቀም የሚከለክለው ህጉ የወጣው በቀድሞዋ የአገሪቱ መሪ ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ የስልጣን ዘመን እንደነበር ያስታወሰው ዘገባው፤ ባለፈው አመትም በጸጉር ምርቶች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ መጣሉን አስታውሷል፡፡


Read 2735 times
Administrator

Latest from Administrator