Print this page
Sunday, 21 October 2018 00:00

ኢንተርኔት ለደቡብ አፍሪካውያን ሰብዓዊ መብት መሆን አለበት ተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የኢንተርኔት አቅርቦትን በእኩልነት መጠቀም ለደቡብ አፍሪካውያን ዜጎች እንደ አንድ መሰረታዊ የሰብዓዊ መብት መቆጠር እንዳለበት ሚዲያ ሞኒተሪንግ አፍሪካ የተባለ ተቋም ጠይቋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ በአገሪቱ በተካሄደ ስብሰባ ላይ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ዊሊያም በርድ ለአገሪቱ መንግስት ባስተላለፉት መልዕክት፤ የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ለደቡብ አፍሪካውያን ሰብዓዊ መብት መሆን እንደሚገባው መናገራቸውን ሜይል ኤንድ ዘጋርዲያን ዘግቧል፡፡
የደቡብ አፍሪካ መንግስት በተለይ ለድሃ ዜጎቹ መረጃዎችን የሚያገኙበትና የሚለዋወጡበት ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት አቅርቦት ያለምንም ገደብና መቋረጥ ካላቀረበ፣ አገሪቱ ወደ አፓርታይድ ዘመን መመለሷ አይቀሬ ነው ሲሉም ተናግረዋል፤ ዳይሬክተሩ፡፡
በአገሪቱ የኢንተርኔት አገልግሎት ክፍያ እጅግ ውድ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ሃብታሞች ገንዘብ ከፍለው ቢጠቀሙም ከአገሪቱ የህዝብ ቁጥር አብላጫውን የሚይዙት ድሃ ዜጎች ግን አገልግሎቱን ለመጠቀም የማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኙ አመልክተዋል፡፡

Read 1161 times
Administrator

Latest from Administrator