Print this page
Saturday, 29 September 2018 13:46

ሴቶች በግላቸው እራሳቸውን…

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ሴቶች በተፈጥሮአቸው ከሚኖራቸው የስነተዋልዶ ባህርይ አንዱ የወር አበባ ነው፡፡ ሴት ልጆች በአስራዎቹ እድሜ ክልል ሲደርሱ የሚያዩት የወር አበባ የሚፈጠረው የማህጸን ግድግዳ ጽንስ ይፈጠራል ከሚል ከተዘጋጀ በሁዋላ ጽንሱ መፈጠሩ ሲቀር ይፈራ ርስና ወደፈሳሽነት ተለውጦ ንጹህ ያልሆነ ደም ይፈሳል፡፡ የወር አበባ የሚቆየው ከ3-5 ቀን ድረስ ነው፡፡ የወር አበባ ተፈጥ ሮአዊ ሲሆን በመፍሰሱ ምክንያት በሰውነት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት የሌለው ሲሆን በትክክ ለኛው ሁኔታ ካልፈሰሰ ግን በመጠኑ ያለመመቸትና የሕመም ስሜት ሊያስከትል ይችላል፡፡ በእ ርግጥ አንዳንድ ሴቶች በከፍተኛ ሁኔታ የሕመም ስሜት እንዳላቸው ይናገራሉ፡፡
የወር አበባ በሚመጣበት ወቅት የሚከሰተው የህመም ስሜት በሁለት ይከፈላል፡፡
primary dysmenorrhea፡- ይህ አይነቱ የህመም ስሜት በ90% ያህል ሴቶች ላይ የሚከሰት ሲሆን ይህ በአብዛኛው ሴቶቹ ሲያገቡ ወይም ልጅ ሲወልዱ መፍትሔ የሚያገኝ ነው፡፡
secondary dysmenorrhea ፡- ይህ ሁለተኛው የሕመም አይነት ሲሆን በዳሌ አካባቢና ከማህጸን ጋር በተያያዘ የሚከሰት ሕመም ነው፡፡ በእርግጥ መፍትሔው የሚገኘው የሚያማቸው ሴቶች በሕክምና ከተረዱ ነው፡፡
አንዳድ ሴቶች የወር አበባ በወር ሲመጣ ቀኑን ሳያስተካክል የሚመጣ መሆኑን ሲገልጹ ሌሎች ደግሞ በፍሰቱ የማነስና የመብዛት ሁኔታን ያስተውላሉ፡፡ ነገር ግን የወር አበባ የሚበዛባቸው ሴቶች ልብ ሊሉት የሚገባቸው ነገር አለ፡፡
በተፈጥሮ ጭንቀታም መሆን፤
በማህጸን ዙሪያ እጢ ወይንም ኢንፌክሽን ካለ እና ሌሎች ተያያዥ በሆኑ ምክንያቶች የወር አበባ በሚመጣበት ጊዜ መብዛትንና ሕመምን ሊያስከትል የሚችል መሆኑን ነው፡፡
ከወር አበባ ጋር በተያያዘ ሕመም ይሰማናል የሚሉ ሴቶች የሚገልጹትን ስሜት ከአንዲት ሴት በደረሰን መልእክት መመልት ይቻላል፡፡
‹‹…እኔ በእድሜዬ ወደ 32/ሰላሳ ሁለት አመት ይሆነኛል። የወር አበባ ከመጀመሪያውም እንደሌሎች ሴቶች በወቅቱ ወይንም በቶሎ ያላየሁ ሲሆን መምጣት የጀመረው በ18/አመት እድሜዬ ነው፡፡ ከዚያ ጊዜ ጀምሮም ልክ በወር አንድ ጊዜ ታማሚ ሆኛለሁ፡፡ አስቀድሞውኑ የሚጀምረኝ ሕመም አለ፡፡ ወገቤን ይከተክተኛል፤ማህጸኔ አካባቢ ጨምድዶ ይይዘኛል፤ የእራስ ምታት ጭምር ስለሚያመኝ በዚህ ጊዜ ሰው ባያናግረኝ እመርጣለሁ፡፡ ይህንን ሁኔታ ባለቤቴ ለረጅም ጊዜ ሊረዳው አልቻለም ነበር፡፡ እንዲያው አመልሽ ተለውጦ እንጂ የወር አበባ መም ጣት ባንቺ ብቻ አልተጀመረም ይለኝ ነበር። ነገር ግን አንድ ጊዜ …ተነሽና ወደሐኪም ቤት እንሂድ አለኝ፡፡ እኔም እሺ ብዬ ሔድኩ፡፡ ሐኪሙ እሱንም እኔንም አስቀምጦ ሁኔታውን ሲያ ስረዳ እዚያው ሐኪሙ ፊት ነበር ይቅርታ የጠየቀኝ፡፡ ከዚያ በሁዋላ ባለቤቴ በደንብ ይረዳኝ ጀመር፡፡ ባል አግብቼም ሆነ ልጅ ወልጄ ሕመሙ ግን አልተሻለኝም፡፡››
    ቤተልሔም ብስራት ከቤተል
በአንድ ወቅት ያነጋገርናቸው የማህጸንና ጽንስ ሕክምና እስፔሻሊስት ዶ/ር መብራቱ ጀምበር የሚከተለውን ብለው ነበር፡፡
…ከወር አበባ ጋር በተያያዘ የሚከሰተውን የህመም ስሜት በተለያየ መንገድ መግለጽ ይቻላል፡፡ ለሕክምና የሚመጡት ሴቶች እንደሚገልጹት ከሆነ የጡት ሕመም፤ የእራስ ምታት፤ የእግር ማበጥ፤ በወገብና በማህጸን አካባቢ የሚሰሙ ሕመሞች የመሳሰሉትቸ  ሊከሰቱ ይችላሉ፡፡ ለምሳሌም የማህጸን በር ጠባብ ከሆነ የሚፈሰውን ደም እንደልብ ስለማያስተላልፍ ማህጸን ደሙን ለማስወጣት ሲል በሚያደርገው ትግል በሴቶቹ ላይ ሕመም ሊያስከትል ይችላል፡፡ ይህ አይነቱ ሕመም ምንም አይነት ምክንያት ሳይኖር የሚፈጠር የህመም ስሜት ሲሆን እንደእጢ የመሳሰሉ ችግሮች ባሉበት ሁኔታ ግን ምክንያታዊ የሆነ ሕመም ነው፡፡ በእርግጥ ብዙውን ጊዜ ከወር አበባ ጋር ተያይዞ የሚከሰት ችግር በጋብቻ እና ልጅ በመውለድ ምክንያት ሊወገድ የሚችል ሲሆን አንዳንድ ሴቶች ላይ ያለው አጋጣሚ ግን መድሀኒት ከመውሰድ እስከ ቀዶ ሕክምና የሚያደርስ ሕክምና ሊያስፈልጋቸው የሚችል ይሆናል፡፡ ነገር ግን የወር አበባን ለማስወገድ ሲባል ብቻ ጋብቻ እና ያልተፈለገ እርግዝና እንዳይኖር መጠንቀቅ እንደሚያስፈልግ በወቅቱ ዶ/ር መብራቱ ጀምበር ገልጸው ነበር፡፡
በወር አበባ ጊዜ ለሚከሰት ሕመም እንደማስታገሻ ከሚታሰቡት መካከል የአመጋገብ ሁኔታዎ ችም ቸል የማይባሉ ናቸው፡፡ አንዳድ ሴቶች እንደሚመሰክሩት የአመጋገብ ሁኔታን በመለወጣ ቸው ምክንያት ሕመሙ እንደታገሰላቸው ያሳያል፡፡ የአስተሳሰብ ሁኔታን ለማስተካከል የሚረዱ እንቅስቃሴዎች ለምሳሌም እንደ ዮጋ የመሳሰሉት ሊረዱ ይችላሉ፡፡
አመጋገብ፡-
በካልሲየም የበለጸጉ ምግቦችን መመገብ… ባቄላ፤ ጥቁር አረንጉዋዴ ቀለም ያላቸው አትክልቶች እንደ..ጎመን የመሳሰሉ ..ወዘተ…
ከሰውነት ውስጥ መመረዝን የሚያስወግዱ ምግቦችን መመገብ…ፍራፍሬዎች… ቲማቲም…ወዘተ…
ተፈጥሮአዊ ይዘታቸውን የለወጡ… እንደ የተፈተገ ስንዴ ከመሳሰሉ የሚሰሩ ምግቦችን … ነጭ ዳቦ… ፓስታ እና ስኩዋር የመሳሰሉትን አለመመገብ…
ቀይ ስጋን መመገብ አለማብዛት እና በቀዝቃዛ ውሀ ውስጥ የሚገኝ አሳን እንዲሁም ፕሮቲን ለማግኘት የሚረዳውን እንደ ባቄላ የመሳሰሉትን መመገብ…
ጤናማ የሆኑ የአትክልትና የወይራ ዘይት መጠቀም…
በአመጋገብ ውስጥ የአኩሪ አተር ወተትን ማካተት፤ ስብ ያላቸውን ምግቦች መቀነስ፤
በንግድ ሱቆች የተደረደሩ …ተዘጋጅተው የሚሸጡ እንደ ኩኪስ፤ ኬኮች፤ የተጠበሰ ድንች፤ እና ባጠቃላይም በኢንደስትሪ ተሰርተው የሚቀርቡ ምግቦችን እና ቅቤ የመሳሰሉ ትን ነገሮች አለመመገብ…
እንደ ቡና ያሉ፤ አልኮሆል እና ሲጋራ ማጤስ የመሳሰሉትን ከልምድ ማስወገድ…
በቀን ከ6-8/ብርጭቆ የተጣራ ውሀ መጠጣት…
በቀን ውስጥ ለ30/ደቂቃ ያህል በሳምንት ለ5/ቀናት የአካል ብቃት እንቅስቃሴ መስራት፤
ከላይ የተጠቀሰው የአመጋገብ ልማድ ለማንኛውም ሰው የሚመከር ሲሆን በተለይም የወር አበባ በሚመጣበት ወቅት ሕመም የሚሰማቸው ሴቶች አመጋገባ ቸውን በተቻለ መጠን በተጠቀሰው መልክ ማስተካከል ቢችሉ ሕመሙ እንደሚቀንስላቸው መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ከዚህ በተጨ ማሪም አመጋገብን ለመደገፍ ሲባል ከሚወሰዱ መካከል የሚከተሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡
ኦሜጋ -3/ ለምሳሌ የአሳ ዘይት በቀን 6/ግራም ቢወሰድ በወር አበባ ጊዜ የሚሰማውን ሕመም ሊቀንስ ይችላል፡፡ ነገር ግን ለምሳሌ እንደ ደም ማቅጠኛ ያሉ መድሀኒቶችን ለሚወስዱ ሰዎች አደገኛ ሊሆን ስለሚችል ሐኪምን አስቀድሞ ማማከር ይገባል፡፡  
ካልሲየም በወር አበባ ጊዜ የሚከሰትን ሕመም ከማስታገስ በተጨማሪ ለጤናማ አጥንት እና ጡንቻዎች መገንባት አስፈላጊ ነው፡፡ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ካልሲየም ሲትሬት ማለትም በካልሲየም መልክ የተሰራው ሰውነት በቀላሉ የሚቀበለው ስለሆነ የወር አበባ ሕመምን ለማስታገስ ይረዳል፡፡ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ግን የወር አበባው ከጀመረ በሁዋላ ቢወሰድ ጥቅም ላይሰጥ ይችላል፡፡
በአጠቃላይም ቫይታን ዲ፤ ቫይታሚን ኢ፤ እና ማግኔዥየም የወር አበባ ከመጀመሩ አስቀድሞ ቢወሰድ የህመም ስሜትን ሊቀንሱ እንደሚችሉ መረጃው የሚጠቁም ሲሆን ለማንኛውም ግን ሐኪምን ማማከር እንደሚጠቅም ይገልጻል፡፡
የወር አበባ ሕመም የሚሰማቸው ሴቶች በግላቸው እራሳቸውን መርዳት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሙቀት እንዲሰማቸው ማድረግ፤ጀርባን ጫን ጫን እያሉ መግፋት ወይንም እንደመታሸት ማድረግ፤ ሴትየዋ የህመሙ ስሜት እንዳይሰማት ማረሳሳት፤ሕመሙን እረስታ እንድትረጋጋ ማድረግ፤ የመሳሰሉት ዘዴዎች ይጠቅማሉ፡፡
ከዚህ ውጭ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ በወር አበባ ወቅት ለሚሰማ ሕመም ማስታገ ሻነት ብቻ ሳይሆን በማንኛውም ወቅት የሚጠቅም በመሆኑ የእግር ጉዞን ጨምሮ ሌሎች እንቅ ስቃሴዎችን ማድረግ ለጤናማነት ይረዳል፡፡

Read 3931 times
Administrator

Latest from Administrator