Monday, 10 September 2018 00:00

የ8ኛው ዙር የለዛ ሽልማትምርጥ አምስቶች ታወቁ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በቀጣዩ ጥቅምት 13 ቀን 2011 በሂልተን ሆቴል ለሚካሄደው “ለዛ” የአድማጮች ምርጫ ሽልማት ለመጨረሻ ዙር ያለፉ ምርጥ አምስቶች ታወቁ፡፡ በዚህም መሰረት በየአመቱ ምርጥ ፊልም ዘርፍ “ወደኋላ”፣ “እርቅይሁን”፣ “በእናት መንገድ”፣ “ትህትናና” “ድንግሉ” ሲያልፉ በምርጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ፊልም ዘርፍ ደግሞ “ምን ልታዘዝ”፣ “ዘመን”፣ “ሰንሰለት”፣ “ደርሶ መልስ” እና “ቤቶች” ተመርጠዋል፡፡ በአመቱ ምርጥ ተዋናይ ዘርፍ አለባቸው መኮንን በ“ትህትና”፣ እንግዳሰው ሀብቴ በ“ሰራችልኝ”፣ ሔኖክ ወንድሙ በ“የፈጣሪ ጊዜ”፣ አለማየሁ ታደሰ በ“ድንግሉ” እና ኤርሚያስ ታደሰ በ“ታላቅ ቅናሽ” ማለፋቸውን የሽልማቱ አዘጋጅ ለዛ ሾው አስታውቋል፡፡
በየዓመቱ ምርጥ ተዋናይት ዘርፍ አዚዛ አህመድ በ“ትህትና” ዕፀህይወት አበበ በ“አስነኪኝ”፣ ሊዲያ ተስፋዬ በ“ወደኋላ”፣ አዲስአለም ጌታነህ በ“ሀ እና ለ 2”፣ እንዲሁም ፍናን ህድሩ በ“እርቅ ይሁን” ተመርጠዋል፡፡ በምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ ዘርፍም “የቤት ሥራ”፣ “የመጀመሪያዬ ነው”፣ የቴዲዮ “ሎኦ ሎኦ” “ትርታዬ”፣ የአቢ ላቀው “ሆዴን ሰው ራበው”ና የሄለን በርሄ “ፊት አውራሪ” ምርጥ አምስት ውስጥ ተቀላቅለዋል፡፡
በየዓመቱ ምርጥ አልበም ዘርፍ፣ የናቲማን ቁጥር 2 አልበም፣ የእሱባለው ይታዬው “ትርታዬ” የሮፍናን “ነፀብራቅ”፣ የብስራት ሱራፌል “ቃል በቃል”፣ የሄለን በርሄ “እስኪ ልየው”ና የጃኖ ባንድ “ለራስህ ነው” ሲያልፉ በምርጥ ነጠላ ዜማ ዘርፍ የሮፍናን “ጨረቃን” የያሬድ ነጉ “ዘለላዬ”፣ የአቡሽ ዘለቀና ቤኪግዕዝ “ማሎ ኢንተሎ”፣ የብስራት ሱራፌል “የቤት ሥራ” እና የናቲ ማን “የመጀመሪያዬ ነው” ወደመጨረሻው ዙር አልፈዋል፡፡
የመጨረሻውን ተሸላሚ ለመምረጥ በwww.lezashow.com ገብተው የሚያደንቁትን አርቲስት፣ ፊልም፣ ሙዚቃ ወይም ቪዲዮ መምረጥ እንዲችሉ የለዛ የሬዲዩ ፕሮግራም አዘጋጅ ጋዜጠኛ ብርሃኑ ድጋፌ ጥሪ አቅርቧል፡፡

Read 7050 times