Monday, 10 September 2018 00:00

የአመፃ ልጅ” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(8 votes)


    ታዋቂው ደቡብ አፍሪካዊ ኮሜዲያን ትሬቨር ኖዋህ በቅድመና ድህረ አፓርታይድ ስላሳለፈው የልጅነት ጊዜው ከፃፈው “Bora a crime stories from a south African childhood” ከተሰኘው መጽሐፍ የአመፃ ልጅ በሚል ወደ አማርኛ የተተረጐመው መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡
በጥላሁን ግርማ የተተረጐመው ይሄው መፅሐፍ የአፓርታይድን አስከፊነት በቀልድና በምፀት እያዋዛ ለአንባቢው የሚያቀርብ ሲሆን፤ በመፅሐፉ ውስጥ የደራሲው እናት ሥርዓቱን በመፋለም ሕግ ጥሳ ከነጭ የወለደችውን ልጅ እንዴት እንዳሳደገችውና ጐን ለጐንም የዘረኝነትን አስከፊነት በተለያዩ የመፅሐፉ ምዕራፎች ውስጥ እንደሚያስቃኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ በ256 ገፅ የተቀነበበው መፅሐፉ በ130 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 6145 times