Print this page
Saturday, 01 September 2018 15:36

በደቡብ ኮርያ ትምህርት ቤቶች ቡና መሸጥ ሊከለከል ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የደቡብ ኮርያ መንግስት ተማሪዎችንና መምህራንን ቡና አብዝቶ ከመጠቀም ጋር ተያይዘው ከሚከሰቱ ችግሮች ለመጠበቅ በሚል በትምህርት ቤቶች ቅጽር ግቢ ውስጥ ቡና እንዳይሸጥ የሚከለክል ህግ ሊያወጣ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
የአገሪቱን የምግብና የመድሃኒት ደህንነት ሚኒስትር መግለጫን ጠቅሶ ዘገባው እንዳለው፣ በሁሉም የአገሪቱ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ከመጪው መስከረም ወር ጀምሮ ቡና ሲሸጥም ሆነ ሲገዛ የተገኘ ከፍተኛ ቅጣት ይጣልበታል፡፡
መንፈሳቸውንና ዘና ለማድረግና ለመነቃቃት በማሰብ በርካታ ተማሪዎችና መምህራን በትምህርት ቤቶች ውስጥ ቡና በብዛት እየተጠቀሙ የልብ ምት መጨመርና የእንቅልፍ ማጣትን ጨምሮ ለተለያዩ የጤና እና የስነልቦና ችግሮች እየተጋለጡ መሆናቸው አሳስቦኛል ያለው ሚኒስቴሩ፣ ይህን ችግር ለመቅረፍ በቡና ሽያጭ ላይ ክልከላ ለማድረግ መወሰኑን አስታውቋል፡፡
በመዲናዋ ሴኡል ከ18 ሺህ በላይ የቡና መሸጫዎች እንዳሉና አንድ ደቡብ ኮርያዊ በአመት በአማካይ 181 ሲኒ ቡና ይጠጣል ተብሎ እንደሚገመት የጠቆመው ዘገባው፣ ይህም አገሪቱን ከእስያ ከፍተኛው የቡና ተጠቃሚነት ያለባት አገር ያደርጋታል ብሏል፡፡

Read 3804 times
Administrator

Latest from Administrator