Saturday, 01 September 2018 15:35

9ኛው ሰምና ወርቅ የኪነ ጥበብ ምሽት ሐሙስ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

  ዘጠነኛው ዙር ሰምና ወርቅ የኪነ ጥበብ ምሽት በልዩ የበዓል ፕሮግራም ዝግጅት የፊታችን ሐሙስ በቫምዳስ የመዝናኛ ማዕከል ከ11፡30 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
በዕለቱ ዶ/ር ብርሃኑ ግዛው፣ አርቲስት አዜብ ወርቁ፣ ወግ አዋቂው በኃይሉ ገ/መድኅን፣ አንጋፋዋ ብዕረኛ መቅደስ ጀምበሩ፣ ገጣሚዎቹ ኤፍሬም ስዩም፣ ትዕግስት ዓለምነህ፣ የሺመቤት ካሳ፣ መምህርት እፀገነት ከበደና በቅርቡ ከአሜሪካ የመጡት አርቲስት ተክሌ ደስታና ደራሲና ጋዜጠኛ አለማየሁ ገ/ህይወት ተገኝተው ምሽቱን እንደሚያደምቁት ታውቋል፡፡ የኪነ ጥበብ ዝግጅቱ መሶብ ባህላዊ ባንድ እንደሚታጀብም የሰምና ወርቅ የኪነ ጥበብ ምሽት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው አለሙ ገልጿል፡፡

Read 4912 times