በመምህር ገላውዴዎስ አለልኝ የተዘጋጀው “ፈረንሳይኛ ቋንቋን ያለአስተማሪ” መፅሐፍ ሰሞኑን ለገበያ ቀርቧል፡፡
አዘጋጁ መፅሀፉን ያሰናዱበትን ምክንያት ሲገልፅ፤ “ይህንን መፅሐፍ ለመፃፍ ሳስብ የኔ መፅሐፍ ከሌሎች መፃህፍቶች በተለይ መንገድ እውቀትን ያካፍላል ብዬ ሳይሆን በተለይ አማርኛ ለሚያነቡ ምንም ሳይቸገሩ በቀጥታ ወደ ንግግርና ንባብ ይመራቸዋል በሚል እሳቤ መሆኑ ይታወቅልኝ” ብሏል በመግቢያው ላይ፡፡
በ353 ገፆች የተዘጋጀው መፅሐፉ፤ ለአገር ውስጥ በ155 ብር፣ ለውጭ አገራት ደግሞ በ10 ዶላር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Saturday, 01 September 2018 15:29
“ፈረንሳይኛን ቋንቋ ያለአስተማሪ” እየተሸጠ ነው
Written by ናፍቆት ዮሴፍ
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና