Print this page
Saturday, 01 September 2018 15:06

የሃዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ 100 ግለሰቦች ተከሰሱ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከወር በፊት በሃዋሳ ከተከሰተው የወላይታና ሲዳማ ብሄር ተወላጆች ግጭት ጋር በተያያዘ የሃዋሳ ከተማ ከንቲባን ጨምሮ 100 ግለሰቦች ላይ ትናንት ክስ ተመሰረተባቸው፡፡
የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ አቶ ቴዎድሮስ ገቢባን ጨምሮ በ100 ተጠርጣሪዎች ላይ ከተመሰረተው ክስ መረዳት እንደሚቻለው፤ በከተማዋ በሲዳማና ወላይታ ብሄረሰቦች መካከል ግጭት እንዲፈጠር በማድረግ፣ ከ10 በላይ ሰዎች እንዲሞቱና በርካቶች እንዲፈናቀሉ አድርገዋል ተብሏል፡፡ ከተማዋ ከንቲባ አቶ ቴዎድሮስ ገቢባ ጋር ከተከሰሱ ባለስልጣናት መካከል የሃዋሳ ከተማ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ይገኙበታል፡፡ በተጨማሪም ስድስት የማረሚያ ቤቱ የስራ ኃላፊዎች በድርጊቱ ተሳትፋችኋል በሚል በአቃቢ ህግ ክስ እንደተመሰረተባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡  


Read 3217 times
Administrator

Latest from Administrator