Print this page
Wednesday, 29 August 2018 00:00

አይሲስ በፑንትላንድ ነጋዴዎች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ ጥሏል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

  የአሸባሪው ቡድን አይሲስ ታጣቂዎች በሰሜን ምስራቅ ሶማሊያ በምትገኘው የፑንትላንድ ግዛት አካባቢዎች በሚንቀሳቀሱ ነጋዴዎችና ኩባንያዎች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ መጣላቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የአይሲስ ታጣቂዎች በአካባቢው በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችና ኩባንያዎች በላኩት አጭር የሞባይል የጽሁፍ መልዕክት፣ “ለቡድኑ በቋሚነት ቀረጥ የማትከፍሉ ከሆነ፣ ለመሞት ዝግጁ ሁኑ” የሚል ማስፈራሪያ መስጠታቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡ አይሲስ ቀረጡን የጣለው በሶማሊያ አንዳንድ አካባቢዎች ተመሳሳይ ቀረጥ በመጣል ገቢ ከሚያገኘው ተቀናቃኙ የአሸባሪ ቡድን አልሻባብ የወሰደውን ልምድ ተመርኩዞ ሳይሆን አይቀርም ያለው ዘገባው፤ አይሲስ በደቡባዊ ሶማሊያ መንግስት ጦር ላይ የሚፈጽመውን ጥቃት እያጠናከረ መምጣቱንና ከአልሻባብ ጋር የነበረው ግጭት እየተባባሰ እንደሚገኝም አመልክቷል፡፡

Read 3648 times
Administrator

Latest from Administrator