Print this page
Sunday, 26 August 2018 00:00

የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኞች ለመጨረሻው የሰላም ስምምነት ተቀጣጥረዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 በደቡብ ሱዳን ላለፉት አምስት አመታት የዘለቀውን የእርስ በእርስ ግጭት በድርድር ለመፍታት ደጋግመው ሲሰበሰቡና ባለመስማማት ሲለያዩ የኖሩት የአገሪቱ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ ከነገ በስቲያ ሰኞ የመጨረሻውን የሰላም ስምምነት ይፈራረማሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዥንዋ ዘግቧል፡፡
ተቀናቃኝ ሃይሎቹ በሰኔ ወር በሱዳን መዲና ካርቱም የሰላም ስምምነት መፈራረማቸውንና ከሁለት ሳምንታት በፊትም ስልጣን ለመጋራት ስምምነት ላይ መድረሳቸውን ያስታወሰው ዘገባው፤ ሶስተኛውንና የመጨረሻውን ስምምነት በመጪው ሰኞ ለመፈራረም ቀጠሮ መያዛቸውን አመልክቷል፡፡
ቀጣዩ ስምምነት ባለፉት ሁለት ስምምነቶች እልባት ባልተሰጣቸውና በእንጥልጥል ላይ በሚገኙ ቁልፍ ጉዳዮች ላይ መግባባት ላይ የሚደረስበትና በአገሪቱ ሰላምን ለማስፈን ተስፋ የተጣለበት እንደሆነም ተነግሯል፡፡
ባለፉት ስምምነቶች መግባባት ላይ ባልተዳረሰባቸው የስልጣን መጋራትና የግዛቶች ድንበር አከላለልን የመሳሰሉ ቁልፍ ጉዳዮችን በውይይት ለመፍታት በተቀናቃኝ ሃይሎቹ መካከል የተደረጉ ጥረቶች ተስፋ ሰጪ እንደሆኑ መነገሩን የጠቆመው ዘገባው፤ የምክትል ፕሬዚዳንቱን ስልጣን በመሳሰሉ አከራካሪ ጉዳዮች ላይም መግባባት ላይ መደረሱን አመልክቷል፡፡

Read 2535 times
Administrator

Latest from Administrator