ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በክፍሉ ታደሰ “ኢትዮጵያ ሆይ ቅፅ 2” መፅሐፍ ላይ ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቤተ መፃሕፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡ ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት የአሀዱ ሬዲዮ ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ አርታኢና ጋዜጠኛ ጥበቡ በለጠና አቶ ኩራባቸው ሸዋረጋ ሲሆኑ መድረኩ በመምህር ሰለሞን ተሰማ ጂ እንደሚመራም ታውቋል፡፡ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ ሚዩዚክ ሜይዴይ ጋብዟል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና