Monday, 27 August 2018 00:00

“ስንደመር” የኪነ ጥበብ ምሽት ሐሙስ ይካሄዳል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(0 votes)

 በምስክር ጌታነው ሚዲያና ፕሮሞሽን አዘጋጅነት የሚቀርበው “ስንደመር” የተሰኘ የኪነ ጥበብ ምሽት የፊታችን ሐሙስ ከቀኑ 11፡00 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር ይካሄዳል፡፡ በዕለቱ ወግ፣ ዲስኩር፣ መነባንብና ሌሎች የወቅቱን የአንድነትና የመደመር መንፈስ የሚያንፀባርቁ ኪነ ጥበባዊ ድግሶች እንደሚቀርቡ የምስክር ጌታነው ሚዲያና ፕሮሞሽን ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ ምስክር ጌታነው ገልጿል፡፡
አርቲስት ፈቃዱ ከበደ ወግ የሚያቀርብ ሲሆን ዲስኩር ደግሞ ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ፣ ሙሃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት፣ ረ/ፕሮፌሰር አበባው አያሌው፣ የሙዚቃ ባለሙያውና የኢትዮጵያ ቱሪዝም ድርጅት ም/ዋና ዳይሬክተር ሰርፀ ፍሬስብሃት ያቀርባሉ፡፡ በአርቲስት ሽመልስ አበራ ደግሞ “ጴጥሮስ ያቺን ሰዓት” በመሶብ ባህላዊ ባንድ ፉከራና ሽለላ ታጅቦ እንደሚቀርብም ታውቋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ ለመታደም 100 ብር የመግቢያ ዋጋ የሚከፈል ሲሆን በአሁን ሰዓት ትኬቶቹ በጃፋር መፅሐፍ መደብር፣ በዮናስ መፅሐፍ መደብር፣ በዓይናለም መፅሐፍት መደብር፣ በሳሚ ካፌና ሬስቶራንት እንዲሁም አራት ኪሎ በሚገኘው ምርፋቅ ካፌና ሬስቶራንት ማግኘት እንደሚቻል ታውቋል፡፡

Read 1903 times