በቀድሞው የኢህአዴግ መስራችና አመራር ያሬድ ጥበቡ የተፃፈው “ወጥቼ አልወጣሁም” የተሰኘ የፖለቲካ መፅሐፍ ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በዋቢ ሸበሌ ሆቴል ይመረቃል፡፡
ከ1983-2008 ዓ.ም የነበረውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ በሚያስቃኘው “ወጥቼ አልወጣሁም” መፅሐፍ በምረቃ ሥነ ስርዓቱ ላይ ደራሲያን፣ ገጣሚያን፣ የኪነ ጥበብ ሰዎችና ፖለቲከኞች እንደሚገኙና ኪነ ጥበባዊ ስራዎች እንደሚቀርቡም ለማወቅ ተችሏል፡፡