Print this page
Tuesday, 21 August 2018 00:00

ቬና ለኑሮ ምቹ በመሆን የዓለማችን ቀዳሚዋ ከተማ ሆናለች

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 የአለማችንን ከተሞች የመሰረተ ልማት አውታሮች መሟላት፣ የጸጥታና መረጋጋት፣ የጤና አገልግሎት ጥራት፣ የትምህርት አሰጣጥና ሌሎች መስፈርቶች ተጠቅሞ በመገምገም፣ በየአመቱ ደረጃ የሚሰጠው ኢኮኖሚስት ኢንተለጀንት ዩኒት የተባለው ተቋም፣ ከሰሞኑም የ2018 ለኑሮ ተስማሚና ምቹ የአለማችን ምርጥ ከተሞችን ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ የኦስትሪያዋ ቬና በአንደኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች፡፡
ላለፉት ሰባት ተከታታይ አመታት ለኑሮ ምቹ በመሆን ከአለማችን ከተሞች በቀዳሚነት የዘለቀቺው የአውስትራሊያዋ ሜልቦርን ዘንድሮ ወደ ሁለተኛ ደረጃ ዝቅ ማለቷን የዘገበው ሲኤንኤን፤ የጃፓኗ ኦሳካ በሶስተኛ ደረጃ ላይ መቀመጧን አመልክቷል፡፡
የካናዳዋ ካልጋሪ፣ የአውስትራሊያዋ ሲድኒ፣ የካናዳዋ ቫንኮቨር፣ የጃፓኗ ቶኪዮ፣ የዴንማርኳ ኮፐንሃገንና የአውስትራሊያዋ አዴላዴ እንደ ቅደም ተከተላቸው ከአራተኛ እስከ አስረኛ ያለውን ደረጃ ይዘዋል፡፡ ተቋሙ በዘንድሮው ለኑሮ ምቹ የአለማችን ከተሞች ዝርዝር ውስጥ 140 የተለያዩ የአለማችን አገራት ከተሞችን ያካተተ ሲሆን፣ አውስትራሊያና ካናዳ እያንዳንዳቸው ሶስት ከተሞችን ማስመዝገብ መቻላቸውንም ዘገባው አመልክቷል፡፡
በጦርነት የፈራረሰቺዋ የሶርያ መዲና ደማስቆ በዘንድሮው የአለማችን ከተሞች ዝርዝር ውስጥ በመጨረሻው ደረጃ ላይ የተቀመጠች ለኑሮ እጅግ አዳጋችና አስቸጋሪ የአለማችን ከተማ ስትሆን፣ የባንግላዲሽዋ ዳካ እና የናይጀሪያዋ ሌጎስ 139ኛ እና 138ኛ ደረጃን መያዛቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 5269 times
Administrator

Latest from Administrator