Saturday, 18 August 2018 09:30

45 የጋዳፊ ደጋፊዎች የሞት ቅጣት ተፈረደባቸው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  ታጣቂዎች 2 ሺህ ስደተኞችን ከመጠለያ አባርረዋል

    የሊቢያ ፍርድ ቤት የቀድሞው የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሙአመር ጋዳፊ ደጋፊ የነበሩና ከሰባት አመታት በፊት በመዲናዋ ትሪፖሊ ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ዜጎችን በመግደል በተከሰሱ 45 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ ማስተላለፉ ተዘግቧል፡፡
ለተቃውሞ የወጡ ዜጎችን ገድለዋል በሚል ክስ ከተመሰረተባቸው 128 ሊቢያውያን መካከል ዘጠና ዘጠኙ ጥፋተኛ ሆነው መገኘታቸውን የዘገበው ዥንዋ፤ ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው የትሪፖሊ ፍርድ ቤት ባለፈው ረቡዕ በዋለው ችሎት በ45ቱ ላይ የሞት ፍርድ ውሳኔውን ማስተላለፉን አመልክቷል፡፡
እ.ኤ.አ በ2011 ነሃሴ ወር ላይ የቀድሞውን ፕሬዚዳንት ሙአመር ጋዳፊን ስርዓት ለመቃወም በመዲናዋ ትሪፖሊ አደባባይ የወጡ በርካታ የአገሪቱ ዜጎች በጋዳፊ ደጋፊዎች በአደባባይ አንገታቸውን እየተቀሉ መገደላቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡
በተያያዘ ዜናም፣ የአገሪቱ ታጣቂ ቡድኖች የጋዳፊ ደጋፊ ናቸው ያሏቸውን 2 ሺህ ያህል የአገር ውስጥ ተፈናቃይ ስደተኞችን ትሪፖሊ ከሚገኝ የመጠለያ ካምፕ ማባረራቸውን የተመድ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
ተቋሙ ከትናንት በስቲያ ባወጣው መግለጫ እንዳለው፤ በሊቢያ 192 ሺህ ያህል የአገር ውስጥ ተፈናቃዮች ለአመታት የከፋ ኑሮን በመግፋት ላይ የሚገኙ ሲሆን በተለይም ከአናሳ ጎሳ የተወለዱ ሊቢያውያን በታጣቂዎች ከፍተኛ በደል እንደሚፈጸምባቸው አመልክቷል፡፡

Read 2912 times