በአዲስ አበባ ካዛንቺስ አካባቢ የሚገኘው አልማዝ ላሊበላ ባርና ሬስቶራንት የተመሠረተበትን ሠላሳኛ ዓመት በኪነጥበብ ዝግጅት እንደሚያከብር ገለፀ፡፡ ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት በሚጀመረው አከባበር የባርና ሬስቶራንቱን የሦስት አስርት ዓመታት ጉዞ የሚያሳይ መሰናዶ፣ የሙዚቃ እና ዳንስ ዝግጅትይኖረዋል፡፡ በአልማዝ ላሊበላ ሬስቶራንት የሙዚቃ ሥራዎቻቸውን ያቀርቡ ከነበሩ አርቲስቶች መካከል ኩኩ ሰብስቤ፣ ኤልያስ ተባበል፣ ሐመልማል አባተ እና ብርቱኳን ዱባለ ይገኙበታል፡፡