ሚዩዚክ ሜይዴይ ከኢትዮጵስ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ነገ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ “ተዓምራዊነት፣ ብህትውናና ኪነ ጥበባዊ ሂስ” በተሰኘ መፅሐፍ ላይ በብሔራዊ ቤተ መፃህፍትና ቤተ መዛግብት ኤጀንሲ አዳራሽ ውይይት ያካሂዳል፡፡
ለውይይቱ የመነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የፍልስፍና መምህር አቶ ብሩህ አለምነህ ሲሆኑ መድረኩም በአቶ ሰለሞን ተሰማ ጂ እንደሚመራ ታውቋል፡፡ ፍላጎት ያለው በውይይቱ ላይ እንዲሳተፍ አዘጋጁ ጋብዟል፡፡