Sunday, 05 August 2018 00:00

በህንድ 4 ሚሊዮን ሰዎች ዜግነታቸውን ተነጥቀዋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 ከጎረቤት አገራት በህገወጥ መንገድ እየገቡ ዜግነት የሚያገኙ ስደተኞች ያማረሩት የህንድ መንግስት፣ ሰሞኑን በወሰደው እርምጃ አሳም በተባለው የአገሪቱ ግዛት የሚኖሩ 4 ሚሊዮን ሰዎችን ዜግነት መንጠቁን ዘ ኢንዲፔንደንት ዘግቧል፡፡
ጎረቤት አገር ባንግላዴሽ ነጻነቷን ካወጀችበት እ.ኤ.አ ከ1971 አንስቶ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ባንግላዴሻውያን ወደ ግዛቱ በህገ ወጥ መንገድ እንደገቡ የጠቆመው የህንድ መንግስት፤ በቅርቡ ባደረገው ምርመራ ዜግነታቸውን የሚያረጋግጥ ህጋዊ ሰነድ የሌላቸው 4 ሚሊዮን ሰዎች ማግኘቱን አመልክቷል፡፡
እነዚሁ 4 ሚሊዮን ሰዎች ህንዳውያን መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የሰነድ ማስረጃ እስከ መስከረም ወር መጀመሪያ ድረስ ለሚመለከተው የመንግስት አካል በማቅረብ ዜግነታቸውን እንዲያረጋግጡ ጥሪ ቀርቦላቸዋል ያለው ዘገባው፤ እስከዚያው ድረስ ግን ህገወጥ ስደተኛ ተብለው እንደማይመዘገቡ ቃል እንደተገባላቸው አመልክቷል፡፡

Read 2227 times